Welcome to Lideta Subcity Administration!       እንኳን ወደ ልደታ ክ/ከተማ አስተዳደር በሰላም መጡ!       Baga Gaara Kutaa Magaalaa Lidata Nagaan Dhuftan!

የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት

የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ስርዓት በመዘርጋት በቂና የተሟላ መረጃ ያለው፤ በሁለንተናዊ እድገት ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ህብረተሰብ በመፍጠር ከተማችን አዲስ አበባ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን ለማስቻል የበኩሉን ራዕይ ሰንቆ በመንቀሳቀስ ላይ ነው፡፡ ጽ/ቤቱ በአዋጅ ቁጥር 74/2014 ዓ/ም በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሰረት የተለያዩ የኮሙኒኬሽን አግባቦችን በመጠቀም ዘመናዊ፣ ግልጽ እና ፈጣን ምላሽ መስጠትን ባህሉ ያደረገ የኮሙኒኬሽን ስርዓት በመዘርጋት ላይ ይገኛል፡፡

የኮሙኒኬሽን ዘርፉን በማጠናከር በመንግስትና በህዝብ መካከል ጥራት ያለውና እና ለሁሉም ነዋሪ ተደራሽ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ የህዝቡን ትክክለኛ የመረጃ ፍላጎት በማርካት ተሳትፎና ተጠቃሚነቱን ማሳደግ፣ የሀገራችንና የከተማዋን መልካም ገጽታ መገንባት እንዲሁም በዋና ዋና ሀገራዊና ከተማ አቀፋዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባበትን መፍጠር የሚያስችል ተልዕኮ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ... ተጨማሪ ያንብቡ

ሲፈን ባዩ , የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ
image description

የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የልደታ ክ/ከተማ የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ከተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መነሻ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታትና የለውጥ ሥራዎችን ቀጣይነት ለማረጋገጥ የተቋሙን አገልግሎት አሰጣጥ ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በብቃቱና እና በሥነ-ምግባሩ የተመሰገነ የሰው ኃይል እንዲመራ በማድረግ ለተገልጋዮቹ የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች በአዲስ መልክ በመለየት አደራጅቷል፡፡

በተጨማሪም በጽ/ቤት የሚሰጠው አገልግሎት የተገልጋይ ፍላጎትን ማዕከል አድርጎ ይበልጥ ተደራሽ እንዲሆን ለማስቻል የሚሰጡ የአገልግሎት አይነቶች፣ አገልግሎቱ የሚሰጥበት ስታንዳርድ፣ የሚሰጥበትን ቦታ እና ከተገልጋይ የሚጠበቁ ቅድመ ሁኔታዎችን በግልጽ በዝርዝር በማስቀመጥ የጽ/ቤቱ ሠራተኞች በተቀመጠላቸው ስታንዳርድ መሰረት ፍህታዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲሰጡና ተገልጋዮች ምን ዓይነት አገልግሎት በምን ዓይነት ደረጃ ማግኘት እንደሚገባቸው ግንዛቤ በመፍጠር በዚህም ግልፅነትና ተጠያቂነት እንዲኖር፣ በህዝብና መንግስት መካከል መተማመን እንዲፈጠር፣ ልማትና ዲሞክራሲ እንዲያብብ ትልቅ አስተዋጽኦ አላቸው፡፡ በመሆኑም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በዘላቂት ለመፍታት በምናደርገው ጥረት ባለድርሻ አካላትና ህብረተሱቡ ከጽ/ቤቱ ጎን እንዲቆሙ እናሳስባለን፡፡

ጥያቄ ካልዎት እባክዎ ለመደወል አያመንቱ ወይም ይጎብኙን!!

+251910046729

አድራሻችን:-

የልደታ አስተዳደር ህንጻ 2ኛ ወለል ቢሮ ቁ 205