የጽ/ቤቱ ኃላፊ መልእክት
የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ጠንካራ የኮሙኒኬሽን ስርዓት በመዘርጋት በቂና የተሟላ መረጃ ያለው፤ በሁለንተናዊ እድገት ንቁ ተሳትፎ የሚያደርግ ህብረተሰብ በመፍጠር ከተማችን አዲስ አበባ የአፍሪካ የብልጽግና ተምሳሌት እንድትሆን ለማስቻል የበኩሉን ራዕይ ሰንቆ በመንቀሳቀስ ላይ ነው፡፡ ጽ/ቤቱ በአዋጅ ቁጥር 74/2014 ዓ/ም በተሰጠው ተግባርና ኃላፊነት መሰረት የተለያዩ የኮሙኒኬሽን አግባቦችን በመጠቀም ዘመናዊ፣ ግልጽ እና ፈጣን ምላሽ መስጠትን ባህሉ ያደረገ የኮሙኒኬሽን ስርዓት በመዘርጋት ላይ ይገኛል፡፡
የኮሙኒኬሽን ዘርፉን በማጠናከር በመንግስትና በህዝብ መካከል ጥራት ያለውና እና ለሁሉም ነዋሪ ተደራሽ የመረጃ ፍሰት እንዲኖር በማድረግ የህዝቡን ትክክለኛ የመረጃ ፍላጎት በማርካት ተሳትፎና ተጠቃሚነቱን ማሳደግ፣ የሀገራችንና የከተማዋን መልካም ገጽታ መገንባት እንዲሁም በዋና ዋና ሀገራዊና ከተማ አቀፋዊ አጀንዳዎች ላይ የጋራ መግባበትን መፍጠር የሚያስችል ተልዕኮ ይዞ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛል፡፡ ... ተጨማሪ ያንብቡ
ሲፈን ባዩ , የልደታ ክ/ከተማ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ኃላፊ